volunteer
📅
August 11, 2026
የስልጢ ወረዳ የሲቪክ ድርጅቶችና ማህበራት የጋራ ምክር ቤት በሰነና ቀበሌ ለአቅመ ደካማ እናት የቤት ግንባታ አስጀመረ
የስልጢ ወረዳ የሲቪክ ድርጅቶችና ማህበራት የጋራ ምክር ቤት በሰነና ቀበሌ ለአቅመ ደካማ እናት የቤት ግንባታ አስጀመረ
የስልጢ ወረዳ የሲቪክ ድርጅቶችና ማህበራት የጋራ ምክር ቤት በወረዳው ሰነና ቀበሌ ለአንዲት አቅመ ደካማ እናት የቤት ግንባታ ሥራን በይፋ አስጀምሯል።
ተግባሩ ማህበራዊ አብሮነትን፣ የመረዳዳት ባህልን እና ለተቸገሩ ወገኖች የሚደረግ ድጋፍን የሚያጠናክር መሆኑ ተገልጿል።
በግንባታው ማስጀመሪያ ሥነ-ሥርዓት ላይ የስልጢ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሸምሴ ረዲ እንደገለጹት፣ የህብረተሰብ ችግር የሚፈታው በመንግሥት ጥረት ብቻ ሳይሆን የሲቪክ ድርጅቶች፣ ማህበራትና ህብረተሰቡ በጋራ ሲሳተፉ መሆኑን ጠቅሰዋል።
በመሆኑም የተጀመረው በጎ ተግባር ለሌሎችም ተቋማትና ማህበረሰብ አርአያ እንዲሆን ጥሪ አቅርበዋል።
በዚሁ ወቅት የወረዳው የሲቪክ ድርጅቶችና ማህበራት የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ግርማ ደበበ በበኩላቸው፣ የምክር ቤቱ ዋና ዓላማ ለአቅመ ደካሞች ዘላቂ ድጋፍ በማድረግ ማህበራዊ ኃላፊነትን ማጠናከር እንደሆነ ገልጸው፣ ይህ የቤት ግንባታ ጅምር የተቸገሩ ዜጎችን በተግባር የሚደግፍ የአብሮነት ተምሳሌት መሆኑን አስታውቀዋል።
በቀጣይም ተመሳሳይ የልማትና የበጎ አድራጎት ሥራዎች በስፋት እንደሚከናወኑ ገልጸዋል።
የቤት ግንባታው በሲቪክ ድርጅቶች፣ በማህበራት፣ በመንግሥት አካላትና በህብረተሰቡ የጋራ ትብብር በፍጥነት ተጠናቆ ለተጠቃሚዋ እንዲረከብ የተሳታፊዎች ቁርጠኝነት ተገልጿል።
ነሃሴ 01/ስልጢ ወረዳ ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት
Thank you for reading.
View All News